ከ112ሺ በላይ የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያዎች ሽያጭ እየተከናወነባቸው ነው

Posted in Latest News

ባለስልጣኑ የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያዎችን ቁጥር ለማሳደግ እና ሁሉም የንግድ እንቅስቃሴ በሽያጭ መመዝገቢያ መሣሪያ እንዲሆን በማድረግ በአገራችን ዘመናዊ የንግድ እና የግብር አሰባሰብ ስርዓት ለማስፈን በርካታ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከዚህም መካከል መሣሪያውን ለማቅረብ ለሚጠይቁ የግል ባለሀብቶች በማስተማርና በመደገፍ የአቅራቢነት እውቅና መስጠት ይገኝበታል፡፡ በመሆኑም በተደረገው ጥረት እስከ የካቲት 30/2007 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ 101ሺ ግብር ከፋዮች 112ሺ የሽያጭ መመዝገቢያ መሣሪያዎችን በመጠቀም ላይ መሆናቸውን የታክስ መረጃ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የየካቲት ወር ሪፖርት ጠቁሟል፡፡

 

በኤፍሬም ብላቱ

Visitors: Yesterday 805 | This week 4058 | This month 11000 | Total 121956

We have 27 guests and no members online